Sunday, November 1, 2015

ድህነት ታሪክ የለውም

ድህነት ሕይወት የለውም። ድህነት ታሪክ የለውም። ቅርስም ውርስም ኣይደለም ድህነት። ጥላህ እንጂ ማተብህ ኣይደለም ድህነት። ስላጣህ ደሃ ነኝ፣ ትንሽ ነኝ ኣትበል። በሙሉ ልብ በብርሃኑ ላይ ከቆምክ ድህነት ኣብሮህ ኣይኖርምና። ለድህነት ሕይወትም ልብም እምትሰጠው ኣንተ ነህ። ለእርሱ የገበርከውን ሕይወት ያህል ኣንተ ሕይወት ታጣለህ። ራስህ ሞተህ ድህነት እንዲኖር እምትፈቅድ ኣንተ ማነህ? በፈጠረህ፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ ኣትበለኝ!

No comments:

Post a Comment